የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
ቂርቆስ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት  
  HOME
  ቂርቆስ ዜናዎች
  አጫጭር ዜናዎች
  kirkos
  በክፍለ ከተማው የሚሰጡ አገልግሎቶች
  => አቅም ግንባታ ጽህፈት ቤት
  => ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት
  => ጤና ጽሕፈት ቤት
  => ትምህርት ጽሕፈት ቤት
  => ህግና ፍትህ ጽህፈት ቤት
  => ባህልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት
  => ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽህፈት ቤት
  => ከተማ ልማት ጽህፈት ቤት
  => ሴቶች ጉዳይ ጽህፈት ቤት
  => ንግድና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት
  => ስራ አስፈጻሚ
  ዜና
  About Kirkos InformationOffice
  ቀበሌዎች
  ዜናዎቻችን
  ቂርቆስ ዜና
ስራ አስፈጻሚ
ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት
   አቶ ቢያ ራያ ዋና ስራ አስፈጻሚ

የሰው ኃይል አስተዳደር ደጋፊ የሥራ ሂደት
1. የሠራተኛ ዝውውር
·        የዝውውር ማስታወቂያ ወጥቶ የአመልካቾች ምዝገባ ያደርጋል፣
·        ተመዝጋቢዎችን በመስፈር መሠረት መለየት፣
·        የተለዩትን በሚወጣው መስፈርት መሠረት ማወዳደርና አሸናፊን መለየት፣
·        የዝውውር ውጤት ተገልጾ ተዘዋዋሪው ክሊራንስ እንዲያመጣ ይደረጋል፣
·        የምደባ ደብዳቤ ተስጥቶ ሥራ እንዲጀመር ይደረጋል፣
2. ድልድልና ምደባ
·        የድልድል ወይም ምደባ ደብዳቤ ይቀርባል፣
·        ተደልዳዩ ወይም ተመዳቢው አስፈላጊውን የቅጥር ማስረጃችን እንዲያመጣ ይደረጋል፣
·        የሕይወት ታሪክ
·        የጤናና የፖሊስ ሰርተፍኬት ወይም ተደልዳዩ ቋሚ ሠራኛ ከሆነ ማህደሩን እንዲያመጣ ወይም እንዲያሟላ ይደረጋል፣
3. የሰው ኃይል ማሟላት ቅጥር፣
·        የቅጥር ማስታወቂያ በመረጃ መረብ መልቀቅ በማዕከላዊ ቦታዎች መለጠፍ፣ በፕሬስ እንዲወጣ ማድረግ፣
·        በማስታወቂያው መሰረት ምዝገባ ማድረግ፣
·        መስፈርቱን የሚያሟሉ(የተሻሉ) አመልካቾችን መለየት፣
·        የተመለመለ ዕጩዎች ጥሪ ይደረጋል፤
·        ፈተና ተዘጋጅ ይሰጣል፣ የፈተናው ውጤት ይታረማ፣ ውጤቱ ተለይቶ ቃለ ጉባኤ ተዘጋጅቶ ይፈረማል
·        የውድድር ውጤቱ ማስታወቂያ ይለጠፋል ለአሸናፊዎች ጥሪ ይቀርባል፤
4. ኮንትራት /ጊዜያዊ ቅጥር
የኮንትራ ቅጥር ስምምነት ለኮሚሽን መላክ
·        የቅጥር ማስታወቂያ በመረጃ መረብ መልቀቅ በማዕከላዊ ቦታዎች መለጠፍ፣ በፕሬስ እንዲወጣ ማድረግ፣
·        በመዝገባው መሠረት ማጣራትና ዕጩዎችን መመልመል እንዲሁም ጥሪ ማድረግ
·        ፈተና አዘጋጅተን መፈተን
·        የውድድር ውጤት በማስታወቅያ መለጠፍ
·        አሸናፊውን ውል በመስሞላት የቅጥር ደብዳቤ መስጠትና ወደ ሥራ ማሰማራት፣
  1. የኮንትራት ቅጥር ማራዘም
    • የኮንትራት ቅጥር ማራዘም ጥያቄ ይቀርባል
    • የኮንትራት ቅጥር ማራዘም ቅድመ ሁኔታዎች በሰው ኃይል አስተዳደር ማሟላትና ማረጋገጥ፣
    • የኮንትራት ጥያቄ ስምምነት በመስጠት ውል በማስገባት፣
6. የትምህርትና ሥልጠና ዕጩ ምልመላ፣
·        ትምህርትና ሥልጠና ዕድሎች ማስታወቂያ ወጥቶ ምዝገባ ይደረጋል፣
·        ከተመዘገቡት ውስጥ አሸናፊውን ለመለየት በመስፈርቱ መሠረት ውድድር ይደረጋል፣
·        አሸናፋ ተለይቶ በvirtual team ይወሰናል፣
·        አሸናፊው ዕጩ ለሰው ኃብት ሥራ አመራር የሥራ ሂደት ይላካል፣
·        ለሥልጠና የተመረጡት አስፈላጊውን ፎርማሊቲ አሟልተው ውል እንዲፈርሙ ተደርጎ እንዲሄዱ ያደርጋል፡፡
7. የደረጃ እድገት
·        የደረጃ ዕድገት መስታወቂያ አዘጋጅቶ ማውጣት፣
·        ተወዳዳሪዎችን መመዝገብና የማያሟሉትን መለየት፣
·        ፈተና አውጥቶ መፈተንና አርሞ ውጤቱን በማጠቀለል ቃለ ጉባኤ አዘጋጅቶ ይፈርማል፤
·        በውድድሩ ውጤት መሠረት አሸናፊው እንዲቀርቡ ተደርጎ የደረጃ ዕድገት ደብዳቤ ተዘጋጅ ይሰጣል፣
·        ለሠራተኛው የሥራ ትውውቅ ተደርጎ ሥራ እንዲጀምር ይደረጋል፡፡
8. የሰው ኃይል ማስተዳደር፣ ማብቃትና ማትጋት፣
  ልዩ ልዩ ፈቃዶች
·        በሥራ ሂደቱ ኃላ የተፈረመ የፍቃድ መጠየቂ ቅጽ ተሞልቶ ይቀርባ፣
·        ማህደር /ማስረጃ/ ተጣርቶ የፈቃድ ወረቀት ተሞልቶ ይሰጣል፤
9. የደመወዝ ጭማሪ
·        በመስፈርቱ መሠረት የደመወዝ ጭማሪ የሚያገኙትን ሠራተኞች ማጣራት ተደርጎ ይለያል፣
·        የደመወዝ ጭማሪ ደብዳቤ በኦፊሰር ተዘጋጅቶና ተፈርሞ ለሠራተኛው እንዲደርስ ይደረጋል፣
10. ዲሲፕሊን አፈጻጸም
·        የሥራ ሂደት ባለቤት የዲስፕሊን ክስ ከማረጃ ጋር ለደጋፊው የሥራ ሂደት ያቀርባል፣
·        የሥራ ሂደቱ የክስ ቻርጅን ጽፎ ለዲሲፕሊን ኮሚቴ ያቀርባል፣
·        ኮሚቴው ጉዳዩንነ አይቶ /መርምሮ/ ውሳኔ ይሰጣል፣
·        የተሰጠው ውሳኔ ከቃለጉባኤ ጋር በደጋፊው የሥራ ሂደት ቀርቦ የሥራ ሂደቱ የውሳኔን ደብዳቤ ለሠራተኛውና ለሚሠራበት የሥራ ሂደት ኃላፊ እንዲደርስ ተደርጎ ተግባራዊ ይደረጋል፣
አገልግሎት ማቋረጥ
11. በገዛ ፈቃድ ማቋረጥ
·        ለቃቂው ለሥራ ሂደቱ ኃላፊ ማመልከቻ ያቀርባል፣
·        የሥራ ሂደቱ ኃላፊ በማመልከቻው ላይ ውሳኔ ሰጥቶ ለደጋፊው የሥራ ሂደት ያስተላፋል፤
·        ሠራተኛው ክሊራንስ እንዲጨርስ ይደረጋል፣
·        የሥራ ልምድና መልቀቂያ ተጽፎና ተፈርሞ ለሠራተኛው ይደርሳል፣
12. ከሥራ ገበታ በመጥፋት
·        የሥራ ሂደቱ ባለቤት ሠራተኛው ለ3 ቀናት ሳያሳውቅ ከቀረ ለደጋፊ የሥራ ሂደት ያሳውቃል፣
·        ለሠራተኛው የመጀመርያ ይጥሪ ማታወቂያ ይወጣል፣
·        በመጀመርያ ጥሪው ካቀረበ ሁለተኛ ማስታወቂያ ይወጣል፣
·        በጥሪው ካቀረበ ሰራተኛው እንዲሰረዝ ይደረጋል
13. በጡረታ ማቋረጥ
·        ሠራተኛው ጊዜው ከደረሰ ወይም በገዛ ፈቃዱ ለመውጣት ወይም በሞት ከተለየ ማመልከቻ ሲቀርብ ማስረጃው እንዲጣራ ይደረጋል፣
·        ማስረጃው የሚፈቅድለት ከሆነ ያለውን እረፍትና ጥቅማጥቅም እንዲወስድ ይደረጋል፣
·        ለጡረታ አስፈላጊ የሆኑ ቅጾች ተሞልተውና ፀድቀው ለማህበራ ዋስትና ይላካል፣
14. የማስረጃ ጥያቄ/ የሥራ ልምድ ፣ ለዋስትና ወዘተ…/
·        ማስረጃው የጠየቀው ሰራተኛ ማህደር/መረጃ/ይጣራል፤
·        የጠየቀው መረጃ ተዘጋጅ ይሰጣል፣
·        በጥሪው ካቀረበ ሰራተኛው እንዲሰረዝ ይደረጋል፡፡







 
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት  
  ቂርቆስ ክፍለ ከተማ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
መምረጥ የዜግነት መብት ነው!
 
Facebook 'Like' Button  
 
 
This website was created for free with Own-Free-Website.com. Would you also like to have your own website?
Sign up for free