የነዋሪዎች ፎረም
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ፎረም 5ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሄደ፡፡
ፎረሙ ጉባኤውን ባካሄደበት ወቅት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ኃ/ማሪያም እንደተናገሩት የነዋሪዎች ፎረም አባላት በሀገሪቷ ልማት፤መልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲዊ ስርዓት ግንባታ ውስጥ ከፍተኛ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ሁሉ ምርጫው ሰላማዊና በህዝብ ዘንድ ተአማኒ እንዲሆንም ሊንቀሳቀሱ ይገባል፡፡
የምርጫውን ውጤት ተከትሎ ችግሮችም እንዳይፈጠሩ ከነዋሪዎች ጋር በህብረት ሊሰሩ ይገባል ነው ያሉት፡፡
የኢህአዴግ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኪዳነ ብርሀነ በበኩላቸው በ5ዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ እንዲሆን በየትምህርት ቤቶችና በሌሎች አካባቢዎች የፀጥታ ምክር ቤቶች መዋቀራቸውን ገልፀው ይህም ምርጫውን ሰላማዊ ለማድረግ ያስችላል ብለዋል፡፡
የፎረሙ ስራ አስፈፃሚ አባልና የመልካም አስተዳደር ሰብሳቢ አቶ ምኡዝ ገ/ህይወት እንዳሉትም ፎረሙ በሀገሪቷ ለሚካሄዱ የልማት ተግባራት ቀጣይነት ምርጫው ፍፁም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ለማድረግ በስፋት ተንቀሳቅሷል ነው ያሉት፡፡
ፎረሙን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት ሽልማት የተሰጠ ሲሆን ስለምርጫው ሰላማዊነት የሚገልፅ ባለ7 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል፡፡
ሪፖርተር
ራዚቃ ዲኖ
0913049933
ግንቦት 07 2002ዓ.ም
የምርጫ ቅስቀሳ ተካሄደ
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የቀበሌ13/14 ኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎች በግንቦት 15 2002 ዓ.ም ምርጫ ማራጩ ህዝብ ኢህአዴግን እንዲመርጥ ቀሰቀሱ፡፡
በቅስቀሳው የኢህአዴግን የምርጫ ምልክት የሚያሳዩ በርካታ መኪናዎችና መፈክሮች የነበሩ ሲሆን አባላቶቹ ኢህአዴግን መምረጥ ልማትን መምረጥ ነው፤ኢህአዴግን መምረጥ የተጀመሩ ልማቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው ማስቻል ነው፤የሚሉ መፈክሮችን እያሰሙ በቀበሌው ቀጣና በማዟዟር የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሂደዋል፡፡
በተመሳሳይም በወረዳ 18 የሚወዳደሩት የኢህአዴግ እጩ ኢ/ር አለማየሁ ተገኑ በቀበሌ 20/21 ለሚኖሩ አባላትና ደጋፊዎች የምረጡን ቅስቀሳ ባደረጉበት ወቅት እንዳሉት ኢህአዴግ ብሔር ብሔረሰቦች በሰላም በመከባበርና በመተሳሰብ እንዲኖሩ አስችሏል፤በየጊዜው የሚመረቁና አገልግሎት እየሰጡ ያሉ የሀይል ተቋማት የኢህአዴግን የልማት መስመር ያሳያሉ ብለዋል፡፡
ኢህአዴግ ቢመረጥ የተጀመሩት የልማት መልካም አስተዳደርና ሰላም በሀገራችን ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ያስችላል ብለዋል፡፡ ህዝቡ ድምፁን ለኢህአዴግ እንዲሰጥ በመጠየቅ ጭምር፡፡
በእለቱ ከምርጫ ቦርድ የተወከሉ አካለትም ታዛቢዎች በምርጫው እለት ሊያደደርጉት ስለሚገባቸው ስነምግባሮች አስረድተዋል፡፡
ሪፖርተር
ራዚቃ ዲኖ
ቀን 06/09/02
የቂርቆስ ክፍለከተማ ግብርና ኤክስቴንሽን በዘርፉ በመስራት ላይ ላሉና መሰማራት ለሚፈልጉ አካላት ለ5 ቀናት የሚቆይ ስልጠና በመስጠት ላይ ነው፡፡ ስልጠናው የዘርፉን ጠቀሜታና ምንነት የማስገንዘብ ታለመ መሆኑም ተገልፃDል፡፡
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የከተማ ግብርና ኤክስቴንሽን የስራ ሂደት መሪ አቶ ደስታ ሎሬንሶ የዘርፉን ምንነትና ጠቀሜታ ሲያስረዱ እንደገለጹት የከተማ ግብርና በትንሽ ቦታ ብዙ ምርት የማምረት ዘዴን በመከተል የሚሰራ የአዝርዕት፤የአትክልትና የእንስሳት እርባታ ተዋፅኦ ልማት ነው፡፡
እንደ አቶ ደስታ ገለፃ የከተማ ግብርና ዘርፎች የአትክልት የአዝርዕትና የፍራፍሬ ልማት፤የእንስሳት እርባታ ተዋፅኦ የአፈርና ውሀ ጥበቃ የደን ልማትና የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤ ሲሆኑ በከተማም የምግብ እህል ዋጋን ለማረጋገት ይረዳሉ ብለዋል፡፡
ዘርፉን ለማጠናከር መንግስት ለስራው የሚያስፈልጉ ቦታዎችንና ስልጠናዎችን ማዘጋጀት እንዳለበት ጠቁመው ለህብረተሰቡና ለአንቀሳቃሾች የግንዛቤ ማስጨበጫዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ነው ያሉት፡፡
በክፍለ ከተማው የከተማ ግብርና ኤክስቴንሽን የእንስሳት እርባታ ተዋፅኦና መኖ ልማት ኦፊሰር ወ/ሮ አልማዝ ታደሰ በበኩላቸው ስልጠናው ትኩረት ያደረገው በዶሮ፤የወተት ከብትና የንብ እርባታ አሰራር ላይ ነው ብለዋል፡፡
ለዘርፉ ውጤታማነት የግንዘቤ ማስጨበጫዎችን ከመስጠት ባሻገር የምክር አገልግሎት መስጠትና ቦታዎችን የማመላከት ስራ እየሰሩ እንደሚገኙም ጨምረው ገልፀዋል፡፡
ሪፖርተር
ራዚቃ ዲኖ 0913 04-99-33
ቀን 06/09/02
ኢህአዴግ የጀመረውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ፡፡መራጩ ህዝብ ኢህአዴግን በመምረጥ እንዲተባበርም ተጠይቋል፡፡
በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 15 የሚወዳደሩ የኢህአዴግ እጩ ተወዳዳሪ ወ/ሮ በላይነሽ ተክላይ ከቀበሌ 17/18 ነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡
በውይይቱ ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የውጭ ግንኙነት ኃላፊና በም/ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ አልማዝ መኮንን እንደተናገሩት ከዚህ ቀደም በነበሩት ስርዓቶች የአገራችን ህዝብ መሪውን የመምረጥ መብት አልነበረውም፡፡ ያለ ምርጫውና ያለ ፍላጎቱ በጉልበት የበላይነት ያላቸው መሪዎች ለበርካታ አመታት ሲያስተዳድሩት ቆይተዋል በዚህም የህዝቡን መብት ያለገደብ ሲረግጡ መቆየታቸውን ነው ወ/ሮ አልማዝ የተናገሩት፡፡
በወረዳ 15 ኢህአዴግን ወክለው ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሚወዳደሩት ወ/ሮ በላይነሽ ተክላይ በበኩላቸው ኢህአዴግ በስልጣን በቆየባቸው 18 አመታት በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን አከናውኗል፡፡ ድጅታቸው በተለይም ከ1993 ዓ.ም ወዲህ በመንገድ ልማት በቤቶች ግንባታና እንዲሁም በገጠር በግብርና ዘርፎች በርካታ አበረታች ተግባራትን ፈጽሟል ብለዋል፡፡
በእለቱ የድርጅቱ አባላትና ደጋፊዎች መጪው ጊዜ ከኢህአዴግ ጋር ብሩህ ነው በማለት ደማቅ የጧፍ ማብራት ስነ ስርዓት አከናውነዋል፡፡
ሪፖርተር
ታሪኩ እንዳለ
09 13 27 85 75
ግንቦት 05 2002ዓ.ም
የቂርቆስ ክፍከተማ የስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በመሬትና መሬት ነክ ጉዳዮች ዙሪያ ከነዋሪዎች ጋር ተወያየ፡፡ነዋሪዎች በመመሪያዎች ላይ ያላቸውን ግንዛቤ የሚያጎለብት ውይይት መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
በቂርቆስ ክፍለከተማ የስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የመሬት ግንባታ ፈቃድ አሰጣጥና አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከተማ በቀለ እንደተናገሩት አዲስ አበባ ደረጃዋን የጠበቅችና የአለም አቀፍ ገፅታን የተላበሰች ለማድረግ የከተማ አስተዳደሩ እያደረገ ካለው እንቅስቃሴ በተጨማሪ ህጋዊነት ያላቸውንን የሌላውን ይዞታዎች ስርዓት የሚያስይዝ መመሪያ አውጥቷል፡፡
እንደ አቶ ከተማ ገለፃ በክፍለ ከተማችን ሰነድ አልባ ይዞታዎች ከ4 ሺ በላይ ሲሆኑ በንጉሱ ግዜ የነበሩትን ካርታዎች ጨምሮ ከ7ሺ በላይ መሆናቸውን ገልፀው ለነዚህ ይዞታዎች አስፈላጊውን ማስረጃ በማሰባሰብና ህጋዊ ካርታ ለመስጠት ለመኖሪያ ቤቶች ትንሹ 75 ካሬ.ሜትር ሲሆን ለድርጅቶች ደግሞ 150 ካሬ ሜትር ነው ብለዋል፡፡
ይህም በቀድሞው መመሪያ ካርታ ለመስጠት 150 ካሬሜትር ይጠይቅ የነበረውን ወደ 75 ካ.ሜ ዝቅ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት፡፡
የክፍለከተማው የኢህአዴግ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኪዳነ ብርሀነ በበኩላቸው በመመሪያው ዙሪያ የተዛባ አስተሳሰቦችን ለመቅረፍ የሚያስችል ውይይት በመሆኑ ነዋሪው ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በግልፅ እንዲወያይ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡
ከነዋሪዎችም በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተሰነዘሩ ሲሆን እኛን በመመሪያው ዙሪያ በማወያየታችሁ ተደስተናል፤በአንዳንድ ቀበሌዎች ላይ የመረጃ ስራ ሲሰራ ከቦታው እንነሳለን የሚል ስጋት አለን፤የሚሉት ተጠቃሾች ናቸው፡፡
አስተዳደሩ በሰጠው ምላሽም በአንዳንድ ቦታዎች የሚደረጉ ጥናቶች በአካባቢው የሚገነቡ ግንባታዎች ለማጣራትና የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ግንባታን በማስመልከት መሆኑን ገልፃDል፡፡
የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቢያ ራያ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብም የከተማ አስተዳደሩ የሚያወጣውን ደንቦችና መመሪያዎች ከነዋሪዎች ጋር የሚያወያየው ነዋሪውን ያላሳተፈ ልማት ውጤታማ እንደማይሆን በማመኑ ነው ብለዋል፡፡ነዋሪዎችም ይህን ተገንዝበው ከአስተዳደሩ ጋር በጥምረት እንዲሰሩ ጠይቀዋል፡፡
ሪፖርተር
ራዚቃ ዲኖ- 0913049933
ግንቦት 04 2002 ዓ.ም
የቻርተር ስምምነት
በቂርቆስ ክፍለከተማ የቀበሌ08/09 አስተዳደር የሚዛናዊ የስራ አመራር ውጤት ምዘናን በማስመልከት የስምምነት ቻርተር ከ6ጽ/ቤቶች ጋር ተፈራረመ፡፡
በ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ምርጥ አፈፃፀም ላሳዩ ፈፃሚዎችም ሽልማት ሰጥቷል፡፡
የሚዛናዊ የስራ አመራር ውጤት ምዘና ቻርተሩን ከስድስቱ ጽ/ቤቶች ጋር የተፈራረሙት የቀበሌው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ኃይሉ ሉሌ እንደተናገሩት ተገልጋይ ተኮር የሆነውን የመሰረታዊ የአሰራር ለውጥ የሚያጠናክረና ለውጡ ያልደረሰባቸውን ሂደቶች የሚተካ ስርዓት ነው የሚዛናዊ የስራ አመራር ውቴት ምዘና፡፡
በዚህም አገልግሎት ፈላጊውን ህብረተሰብ ለማገልገል ፈፃሚው የተሳካ ስራ የሚሰራበት ነው ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ አስተዳደር አቅም ግንባታ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘሩ ሰሙር በበኩላቸው ስርዓቱ ስትራቴጂ ዪካሄድበት፤የሚተገበርበትና የሚመዘንበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አመራሩና ፈፃሚው በቁርጠኝነት ከተንቀሳቀሱ አገልግሎት ፈላጊውን ህብረተሰብ የበለጠ ማርካት ይቻላል ነው ያሉት፡፡
የተጀመረው መልካም አስተዳደርና ልማት እንዲቀጥልም ግንቦት 15 የሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊና በህዝብ ዘንድ ተአማኒ እንዲሆን ሰራተኞች የበኩላቸውን እንዲወጡ አቶ ዘሩ ጠይቀዋል፡፡
በእለቱ የሚዛናዊ የስራ አመራር ውጤት ምዘናን ለመተግበር የሚያስችል የመግባቢያ ቻርተር በዋና ስራ አስፈፃሚውና በስድስቱ ጽ/ቤት ኃላፊዎች መካከል የተፈረመ ሲሆን በ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ምርጥ ለሆኑና ዝውውር ላገኙ ፈፃሚዎች የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል፡፡
ሪፖርተር
ራዚቃ ዲኖ
04/09/2002
የደኢህዴን 17ኛ ዓመት በዓል ተከበረ
ኢህኢዴግ ለልማት ለመልካም አስተዳደርና ለሰላም በትጋት እንደሚሰራ ተገለፀ፡፡
በቂርቆስ ክ/ከተማ የቀበሌ 04 የደኢህዴን ኢህአዲግ አባላትና ደጋፊዎች ደኢህዴን የተመሰረገበትን 17ኛ ዓመት በዓል አክብረዋል፡፡
በሀዊ ሆቴል በተከበረው በዓል ላይ የቀበሌው የኢህአዴግ ተወካይ አቶ ይደነቅ ቢተው እንደተናገሩት ኢህአዴግ የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ በስፋት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ የልማት የመልካም አስተዳደርና የዲሞክራሲ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም የኢህአዴግ ጽኑ አቋም በመሆኑ ድርጅታቸው በትጋት እንደሚሰራ ነው አቶ ይደነቅ የተናገሩት፡፡
የቀበሌው ደኢህዴን ኢሀዲግ ተወካይ ወ/ት መቅደስ መለሰ የድርጅቱን መልዕክት ሲያቀርቡ እንደገለጹት ኢህአዴግ የኢትዮጵያን ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች የስልጣን ጥያቄና የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ እንዲመልስ ለበርካታ ዓመታት የመረረ ትግል አድርጓል፡፡ የተጀመረውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ሰላም ወዳድ ወገኖች ሁሉ ኢህአዴግን በመምረጥ አጋርነታቸውን እንዲያረጋግጡ ጠይቀዋል፡፡
በእለቱ የብአዴን የኦህዴድና የህወሃት አጋር ድርጅቶች የአጋርነት መግለጫ ያቀረቡ ሲሆን በአገራችን የተጀመረውን ልማት መልካም አስተዳደርና ሰላም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከደኢህዴን ጋር በጋራ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡
የብሄር ብሄረሰቦች ባህላዊ አለባበስና ውዝዋዜዎችም ለእይታ ቀርበዋል፡፡
ሪፖርተር
ታሪኩ እንዳለ
ግንቦት 03 2002ዓ.ም
በቂርቆስ ክፍለከተማ ፍትህ ጽ/ቤት የደንብ ማስከበርና መቆጣጠር ወሳኝ የስራ ሂደት በአስራአንዱም ቀበሌዎች ለሚገኙ የደንብ አስከባሪዎች፤ፖሊስ አካላትናለየቀበሌዎቹ ፍትህ ጽ/ቤት ሰራተኞች በምርጫ ዙሪያ የግማሽ ቀን ስልጠና ሰጠ፡፡
ሰልጣኞች ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲያልፍ የድርሻውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ተጠቁሟል፡፡
ስልጠናውን በንግግራቸው የከፈቱት የክፍተካመው ም/ዋና ስራ አስፈፃሚና የፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ደቦጭ እንደተናገሩት በሀገራችን በመካሄድ ላይ ያሉት የልማት ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው ሰላም አስፈላጊ ነው፡፡
በመሆኑም ህገ-ወጥ ተግባራትን ከማስቆም ጎን ለጎን ሰላምና ፀጥታን በማስከበር እረገድ የደንብአስከባሪዎችና የፖሊሶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ግንቦት 15 የሚካሄደው ምርጫም በሰላም እንዲጠናቀቅ በስፋት ሊንቀሳቀሱ እንደሚባ ጠቁመዋል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት በፍትህ ጽ/ቤት የደንብ ማስከበርና መቆጣጠር የስራ ሂደት ባለቤት አቶ በእውቀቱ ገበዩ በበኩላቸው የደንብ ማስከበር ስራው በ6 የህገ-ወጥ ተግባራት ላይ የሚያተኩር ሲሆን ከህገ-ወጥ ተግባራቱ ጋር ተያይዘው የሚከሰቱ ሰላምን የማደፍረስ ስራዎችን መቆጣጠር ያስፈልጋል ነው ያሉት፡፡
የደንብ አስከባሪዎች ከሌሎች አካላት ጋር ተቀናጅተው በህገ-ወጥ ተግባራት ላይ እያደረጉ ያለውን እንቅስቃሴ አጠናክረው እንዲቀጥሉ በማሳሰብ፡፡
ሪፖርተር
ራዚቃ ዲኖ
ግንቦት 03 2002ዓ.ም
በቂርቆስ ክፍለከተማ ፍትህ ጽ/ቤት የደንብ ማስከበርና መቆጣጠር ወሳኝ የስራ ሂደት በአስራአንዱም ቀበሌዎች ለሚገኙ የደንብ አስከባሪዎች፤ፖሊስ አካላትናለየቀበሌዎቹ ፍትህ ጽ/ቤት ሰራተኞች በምርጫ ዙሪያ የግማሽ ቀን ስልጠና ሰጠ፡፡
ሰልጣኞች ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲያልፍ የድርሻውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ተጠቁሟል፡፡
ስልጠናውን በንግግራቸው የከፈቱት የክፍተካመው ም/ዋና ስራ አስፈፃሚና የፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ደቦጭ እንደተናገሩት በሀገራችን በመካሄድ ላይ ያሉት የልማት ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው ሰላም አስፈላጊ ነው፡፡
በመሆኑም ህገ-ወጥ ተግባራትን ከማስቆም ጎን ለጎን ሰላምና ፀጥታን በማስከበር እረገድ የደንብአስከባሪዎችና የፖሊሶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ግንቦት 15 የሚካሄደው ምርጫም በሰላም እንዲጠናቀቅ በስፋት ሊንቀሳቀሱ እንደሚባ ጠቁመዋል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት በፍትህ ጽ/ቤት የደንብ ማስከበርና መቆጣጠር የስራ ሂደት ባለቤት አቶ በእውቀቱ ገበዩ በበኩላቸው የደንብ ማስከበር ስራው በ6 የህገ-ወጥ ተግባራት ላይ የሚያተኩር ሲሆን ከህገ-ወጥ ተግባራቱ ጋር ተያይዘው የሚከሰቱ ሰላምን የማደፍረስ ስራዎችን መቆጣጠር ያስፈልጋል ነው ያሉት፡፡
የደንብ አስከባሪዎች ከሌሎች አካላት ጋር ተቀናጅተው በህገ-ወጥ ተግባራት ላይ እያደረጉ ያለውን እንቅስቃሴ አጠናክረው እንዲቀጥሉ በማሳሰብ፡፡
ሪፖርተር
ራዚቃ ዲኖ
ግንቦት 01 2002 ዓ.ም
በምርጫ ዙሪያ የንግዱ ማህበረሰብ ተወያየ
4ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፤ፍትሃዊና በህዝብ ዘንድ ተአማኒ በሚሆንበት ዙሪያ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ተወያዩ፡፡
ውይይቱ በብሔራዊ ቲያትር አደራሽ በተካሄበደት በወቅት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በቂርቆስ ክፍለከተማ ወረዳ 15 የሚወዳሩትና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ በላይነሽ ተክላይ እንደተናገሩት በኢህአዴግ የሚመራው መንግስት የሀገራችን ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመፍታት ባደረገው እንቅስቃሴ በርካታ ለውጦች ተመዝግበዋል፡፡
በዕዝ ኢኮኖሚ የሚመራውን የንግድ ስርዓት በነፃ ገቢያ በመለወጥ ከከፍተኛ እስከ ዝቅተኛ ድረስ ያሉ ባለሀብቶች በነፃነት የሚሰሩበት የገቢያ ስርዓት ተዘርግቷል ብለዋል፡፡
ከ1983 በፊት የግል ባለሀብት እንደልቡ በግሉ መስራት እንደማይችል ያስታውሱት ኃላፊዋ በኢህአዴግ የሚመራው መንግስት ልማታዊ ባለሀብቶች በሀገሪቷ ልማት ውስጥ የበኩላቸውን እንዲወጡ በማድረግ ላይ ነው ያሉት፡፡ኢህአዴግን በመምረጥ ልማቱንና እድገቱን እንዲያቀጥሉት በመጠየቅ ጭምር፡፡
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የንግዱ ማህበረሰብ ሰብሳቢ አቶ መላኩ በዙ በበኩላቸው 1984 4 የነበረው የባለሀብቶች ቁጥር በ2002 ዓ.ም ከ17 ሺ 800 በላይ መድረሱን ተናግረው ይህም የሚያሳየው መንግስት ለባለሀብቱ የፈጠረው ምቹ ሁኔታ ነው ብለዋል፡፡
ከንግዱ ማህበረሰብም በርካታ አስተያየቶችና ጥያቄዎች የተሰነዘሩ ሲሆን ለባለሀብቶች እየተደረገ ያለው እገዛ ቢቀጥል፤መንግስት የሰራውን ልማት ህዝቡ እንዲያውቀው ማድረግ አለበት የሚሉት ሀሳቦች ተጠቃሾች ናቸው፡፡
ሚያዚያ 30 2002ዓ.ም
ወጣቶች በመፋጠን ላይ ያለውን የወጣቶች ዘርፍ ብዙ ተጠቃሚነት ለማስቀጠል ኢህአዴግን እንዲመርጡ የማዕድንና ኢነርጂ ሚ/ር ኢ/ር አለማየሁ ተገኑ ጠየቁ፡፡
በወረዳ 18 የሚወዳደሩት የማዕድንና ኢነርጂ ሚ/ር ኢ/ር አለማየሁ ተገኑና የአ/አ ከተማ የፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ኃ/ማሪያም ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 02/03 ወጣቶች ሊግ አባላት ጋር የተወያዩ ሲሆን የክፍለ ከተማው የትግራይ ተወላጅ ወጣቶችም በምርጫው ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡
በቂርቆስ ክፍለከተማ የኢህአዴግ ጽ/ቤት የፖለቲካል ዘርፍ ኃላፊ አቶ በቀለ ጉዲሳ እንደተናገሩት ውይይቱ 4ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ የወጣቶች ሚና ለማስገንዘብና በምርጫው ስኬታማነት በኢህአዴግ የተያዙ 3 ግቦችን ከወጣቶችን ጋር ለመወያየት ታስቦ ነው፡፡
በወራዳ 18 የሚወዳዳሩት የማዕድንና ኢነርጂ ሚ/ር ኢንጂነር አለማየሁ ተገኑ በበኩላቸው ወጣቶች ለውትድርና ብቻ በመጠቀም አስከፊ ተግባር የፈፀመውን የደርግ ስርዓት ለማስወገድ በጥንካሬ የታገሉት ወጣቶች ናቸው ብለዋል፡፡
ወጣቶቹ በከፈሉት መስዋዕትነት የተገኘውን ሰላምና ዴሞክራሲ ለማስቀጠል ደግሞ ወጣቶች ኢህአዴግን በመምረጥ ሊያረጋግጡት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ኃ/ማሪያም ይህንኑ ነው ያረጋገጡት በኢህአዴግ የሚመራው መንግስት ዘላቂ ሰላም በማረጋገጥ ባለሀብቶች በሀገሪቷ መዋዕለ ንዋያቸውን በማፍሰስ ለውጪ ንግድ ውጤታማነት እንዲሰሩ አድርጓል በማለት፡፡
ወጣቱም የኢህአዴግን ፖሊሲዎች ጠንቅቆ በማወቅ ምክንያታዊ መራጭ መሆን እንደለበት አስገንዝበዋል፡፡
ሪፖርተር
ራዚቃ ዲኖ
ሚያዚያ 30 2002ዓ.ም
አዲሱ ካቢኔ የልማት ስዎችን ጎበኘ
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ አዲስ የተዋቀረው ካቢኔ በክፍለ ከተማው እየተገነቡ ያሉትን የልማት ስራዎችን ጎበኘ፡፡
የወጣት ማዕከላት የጤና ጣቢያ ግንባታ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ወርክ ሾፕና የቀበሌ ማዕከል ግንባታዎች የተጎበኙ ሲሆን የህዝብ አገልግሎት የሚሰጥባቸው ማዕከላት በማጠናከር መልካም አስተዳደርን እውን ማድረግ እንደሚቻል ተገልጻEል፡፡
የክፍለከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቢያ ራያ ከጉብኝቱ በኋላ አንደገለፁት በክፍለ ከተማው አዲስ የተዋቀረው ካቢኔ በክፍለ ከተማው የሚገነቡ ግንባታዎች ምን ደረጃ ላይ እንዳሉ ለማወቅና ውሳኔ በሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ ለመወሰን አንዲቻል ነው ጉብኝት የተደረገው፡፡ ከጉብኝቱ በኋላም በግንባታው ስራ ላይ መጓተት የሚስተዋልባቸውን ስራዎች ችግር በመለየት በወቅቱ እንዲጠናቀቁ ይደረጋል ብለዋል አቶ ቢያ ፡፡
በክፍለ ከተማው የዲዛይንና ግንባታ ጽ/ቤ የግንባታና ክትትል ንዑስ የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ሙሰማ ሙሳ በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ካለፈው ዓመት የተዛወሩና በዚህ ዓመት የተጀመሩ በቅርቡ ተጠናቀው አንደሚመረቁ ገልፀዋል፡፡ የተቀሩት 14 ፕሮጀክቶችም እስከ ጥቅምት 2003 ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ወደ አገልግሎት እንደሚገቡ አቶ ሙሰማ አስረድተዋል፡፡
በክፍለ ከተማው የጤና ማዕከላት ወጣት ማዕከላት ትምህርት ቤቶችና የቀበሌ ማዕከላት በስፋት በማስገንባት በቀጣይ የተቀላጠፈ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለመስጠት እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ አቶ ቢያ ገልፀዋል፡፡
ሪፖርተር
ታሪኩ እንዳለ
09 13 27 85 75
ሚያዝያ 27/2002
የቂርቆስ ክፍለከተማ ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤውን አካሄደ፡፡
ምክር ቤቱ 6 ጽ/ቤት ኃላፊዎችን ከስልጣን ያወረደ ሲሆን የ8 ጽ/ቤት ኃላፊዎችን ሹመትም አፅድቋል፡፡
ጉባኤው በተካሄደበት ወቅት የቂርቆስ ክፍለከተማ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ክቡር እንግዳ አምዴ እንደገለፁት ምክር ቤቱ አስቸኳይ ጉባኤውን ማካሄድ ያስፈለገው በሀገራችን በሚካሄደው 4ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለመወያያትና የአንዳንድ ጽ/ቤት ኃላፊዎችን ሹም ሽረት ለማፅደቅ ነው፡፡
የክፍለከተማው የህዝብ ግንኙነት አማካሪ አቶ ኪዳነ ብርሀነ እንዳሉት ደግሞ ምርጫ 2002 በተሳካ መልኩ እንዲጠናቀቅ የምክርቤት አባላት ሚና ከፍተኛ መሆን አለበት፡፡የመራጮች ምዝገባን በሰላም መጠናነቅ ያስወሱት አማካሪው የምክር ቤት አባላትና ህብረተሰቡ በፅጥታ ጉዳይ ላይ እያደረጉት ያለው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡
የምክር ቤቱን ሁለተኛ አጀንዳ ያቀረቡት የክፍለከተማው የመንግስት ተጠሪ አቶ ብርሀኑ ታደሰ እንዳሉት በክፍለከተማው በግዢ ስራ ላይ በሙስና የተጠረጠሩትን የፀረ ሙስና ኮሚሽን በእስር እንዲቆዩ ካደረጋቸው ግለሰቦች በተጨማሪ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ሊናራቸው ይችላል ብሎ ያላቸውን የጽ/ቤት ኃላፊዎች ከሷል፡፡ በመሆኑም ምክር ቤቱ እነዚህ የጽ/ቤት ኃላፊዎች የአቅም ውስንነት አለባቸው የላቸውን ጨምሮ ክሱ ከኃላፊነታቸው ጋር አስቸጋሪ ይሆናል በማለቱ ከስልጣን እንዲወርዱ ሲወስን በምትካቸውና የተጓደሉ የጽ/ቤት ኃላፊዎችን ሹመት አፅድቋል፡፡
በዚህም አቶ ቢያራያን ዋና ስራአስፈፃሚ፤አቶ ሰለሞን ደቦጭን ም/ዋናስራአስፈፃሚና የፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ ፤አቶ አምሳሉ ተበጀን የአቅም ግንባታ ጽ/ቤት ኃላፊ፤አቶ ኪዳነማሪያም አረጋዊ የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ፤አቶ ነስረዲን ሽፋ የጥቃቅንና አነስተኛ ልማት ኢንተርፕራይዝ ጽ/ቤት ኃላፊ፤አቶ ጥበቡ በቀለን የንግድና ኢንዱስትሪ ጽ/ቤት ኃላፊ፤አቶ ቃሲም ተሾመን የዲዛይንና ግንባታ ጽ/ቤት ኃላፊና ወ/ሮ እመቤት በቀለን የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ በማድረግ ሾሟል፡፡
ምክር ቤቱ የባህልና ቱሪዝም፤የጤና ጽ/ቤትና የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃለፊዎችን ለመሾም አስፈላጊውን ጥናት እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል፡፡
ሪፖርተር
ራዚቃ ዲኖ
ሚያዚያ 27 2002ዓ.ም
የኢህአዴግ ዕጩ ከአባላትና ደጋፊዎቻቸው ጋር ተወያዩ
የወጣቱን ጉልበት ለሽብርተኛነትና ለሁከት ሊጠቀሙ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን ህዝቡ ሊከለክላቸው ይገባል ተባለ፡፡
በቂርቆስ ክ/ከተማ ቀበሌ 08/09 የኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎች ከወረዳ 20 ዕጩ ተወዳዳሪ ወ/ሮ ብርነሽ አባይ ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡
በአዲስ አበባ ቄራዎቻ ድርጅት አዳራሽ በወረዳ 20 ኢህአዴግን ወክለው የሚወዳደሩት ወ/ሮ ብርነሽ አባይ የድርጅታቸውን ዓላማና ማኒፌስቶ ለአባላት ሲያስተዋውቁ እንደተናገሩት ኢህአዴግ በ97 በአዲስ አበባ በህዝብ የተነፈገውን ድምጽ መነሻ በማድረግ በመላው አገሪቱ ምርጫው ተጭበርብሯል የሚል ውዥንብር በመንዛት ወጣቱን ለጥፋት ለመዳረግ የተናቀሳቀሱ ኃይሎች እንደነበሩ አስታውሰው በ2002 ምርጫም በተመሳሳይ መንገድ ስልጣን ለመያዝ የሚያኮበኮቡ ኃይሎች እንዳሉ ተናግረዋል፡፡
ወጣቱን ትውልድ በጥፋት መስመር በማሰለፍ የአገሪቱን ሰላም ሊያደፈሪሱ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን ህብረተሰቡ ሊያቆማቸው ይገባል ብለዋል፡፡
የቀበሌው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ኃይሉ ሉሌ በበኩላቸው በአካባቢው ሰላም እንዲሰፍንና ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ የቀበሌው ነዋሪ የበኩሉን አስተዋጽዖ ማድረግ ይተበቅበታል፡፡ በአካባቢው በህገወጥ መንገድ በመንቀሳቀስ ስልጣን ለመያዝ የሚታገል ማንኛውም ፓርቲ ህዝቡ ሊከላከለው እንደሚገባ አቶ ኃይሉ አሳስበዋል፡፡
በዕለቱ በግንባሩ አባላትና ደጋፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን ወ/ሮ ብርነሽ አባይ ለጥያቄዎቹ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ሪፖርተር
ታሪኩ እንዳለ
09 13 27 85 75
የቀበሌ 13/14 ነጋዴዎች በምርጫ ዙሪያ ተወያዩ
ሚያዝያ 24/2002
የ2002 አገር አቀፍና የክልል ም/ቤት አባላት ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የንግዱ ህብረተሰብ አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚገባው ተገለጸ፡፡
በቂርቆስ ክ/ከተማ ቀበሌ 13/14 የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ምርጫው ሰላማዊ በሚሆንበት ጉዳይ ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡
በአሥታራ ሆቴል መሰብሰቢያ አዳራሽ በተካሄደው የውይይት ፕሮግራም ላይ የቀበሌው ነጋዴዎች ተወካይ አቶ እስፓጋዱስ ስዩሜ እንደተናገሩት ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የንግዱ ማህበረሰብ ፍላጎት ነው፡፡ ሰላም ባለበት ነጋዴው ነግዶ ማትረፍ የሚችልና ንግዱን በአግባቡ የሚመራ በመሆኑ ነጋዴው ህብረተሰብ በአገሪቱ ሰላም እንዲኖር ግፊት ያደርጋል ብለዋል፡፡
የክ/ከተማው ንግድና ኢንዱስተሪ ልማት ጽ/ቤትና የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አስፋው በበኩላቸው ነጋዴው ህብረተሰብ የተስተካከለ የግብይት ስርዓት እንዲኖረው ሰላማዊ አካባቢ ያስፈልጋል፡፡ለዚህም የንግዱ ማህበረሰብ ከመንግስት ጎን በመቆም ለሰላሙ ሊታገል ይገባል ብለዋል፡፡
ነጋዴዎቹ በግብር አሰባሰብና በተጨማሪ እሴት ታክስ አወሳሰን ዙሪያ ጥያቄ ያነሱ ሲሆን የአዲስ አበባ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ በላይነሽ ተክላይ መልስ ሰጥተውበታል፡፡
በእለቱ በወረዳ 21/22 የሚወዳደሩ የኢህአዴግ እጩ ተወዳዳሪ አቶ ሰለሞን ተስፋዬ ራሳቸውን አስተዋውቀዋል በትውውቁ ወቅት አቶ ሰለሞን እንደተናገሩት የኢህአዴግ ፖሊሲ ትንንሹን የንግድ ህብረተሰብ በማበረታታት ወደ ትልልቅና መካከለኛ ነጋዴነት እንዲገቡ የሚያደርግ ፖሊሲ ነው ብለዋል፡፡
ነጋዱዎቹ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ ጥረት ለማድረግ ቃል የገቡ ሲሆን ባለ አምስት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ውይይታቸውን አጠናቀዋል፡፡
ሪፖርተር
ታሪኩ እንዳለ
09 13 27 85 75
የማዕድንና ኢነርጂ ሚ/ሩ ከባለሀብቶች ጋር ተወያዩ
ሚያዝያ 23 2002
በአገሪቱ የተጀመረውን ምቹ የኢንቭስትመንት ሁኔታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ልማታዊ ባከለሃብቱ ኢህአዴግን እንዲመርጥ ተጠየቀ፡፡
በቂርቆስ ክ/ከተማ ቀበሌ 02/03የሚኖሩ ባለሀብቶች ከማዕድንናኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ኢንጂነር አለማየሁ ተገኑ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይቱ ወቅት ባለሀብቶቹ ለሚኒስተሩ ካነሷቸው ጥያቄዎች መካከል በኢትዮጵያ የነዳጅ ማዕድን ፍለጋው በተጠናከረ መልኩ አልተከከናወነም፤የአዲስ አበባ የውሃ ችግር መቼ ይፈታል?የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረትና የመሳሰሉ ጥያቄዎችየተነሱ ሲሆን ኢንጂነር አለማየሁ በሰጡት ምላሽም የነዳጅ ፍለጋው በተጠናከረ መልኩ እየተካሄደ መሆኑንና ወደፊትም ፍለጋው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል፡፡
የአዲስ አበባ የውሃ ችግርን በተመለከተም የከተማዋን የውኃ ችግር ለመፍታት የተለያ የውሃ ማጣሪያግድቦችን በመገንባትችግሩን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረትን በተመለከተም በቅርቡ የጣና በለስ ፕሮጄክት ስራ ሲጀምር ችግሩ እንደሚቃለል ሚንስተሩ አብራርተዋል፡፡
በቀበሌ 02